Share
Tweet
Pin
Email
Share
Share
Share

ወደ ዱባይ የሚጓዙ መንገደኞች

  • 11/05/2021

ከሚያዝያ 30 ጀምሮ ወደ ዱባይ የሚጓዙ መንገደኞች ከኮቪድ የነጻ የምርመራ መግለጫ ሰርተፊኬት ኪው አር ኮድ (QR code) ወይም ኤሌክትሮኒክ መግለጫ ፊት ለፊት በሚታይ መልኩ የሌለው ከሆነ ተቀባይነት እንደማይኖረውና ለጉዞ ብቁ እንደማያደርግ ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ጤና ጥበቃ ሚኒስተር አስታውቋል። ኪው አር ማረጋገጫው የመንገደኛውን ሙሉ ስም እና ውጤት በኮምፒዩተር ኮድ የሚገልፅ ነው፡፡

ስለሆነም የኮቪድ ምርመራ የሚያደርጉበት የህክምና ተቋም የነጻ ሰርቲፊኬት መግጫው ላይ የኪው አር ኮድ (QR code) የተደገፈ ማረጋጫ መስጠት አለበት፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ ይህን አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ተቋማት ያሉ ሲሆን እስከአሁን የሚከተሉት የምርመራ ተቋማት ይህንኑ አገልግሎት ይሰጣሉ፣

1. International Clinical Laboratories (ICL)

2. Amin General Hospital

3. Washington Medical Centre

4. ICMC General Hospital

እነዚህን ሊወዱ ይችላሉ

TripAdvisor

Ratings and Reviews Powered by TripAdvisor